የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በሁሉም አኅጉረ ስብከት ዘንድ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለመመስረት ለሚሰማሩ ምሁራን ስልጠና ሰጠ
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በመላ ሀገሪቱ በሁሉም አኅጉረ ስብከት ዘንድ ሀገረ ስብከት አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት /ሕብረት/ ለማቋቋምና ከዚህም አንድነት ውክልና የተሰጣቸው ወጣቶች በሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች መደበኛ ዓመታዊ ጉባኤ ዘንድ ተገኝተው በመሪ ዕቅዱ ለመጨረሻ ጊዜ ተወያይተው በማጽደቅ በከፍተኛ የወጣት ንቅናቄ ወደ ሥራ ለመግባት እንዲያስችለው ይህንን መርሐ ግብር በአግባቡ ለሚመሩ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት፣ ከአራቱም የአዲስ አበባ አኅጉረ ስብከትና ከአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ሰ/ት/ቤቶች የተውጣጡ ወጣቶች ከመሪ ዕቅድ ጀምሮ እስከ አፈጻጸሙ ድረስ እንዲሁም በየአኅጉረ ስብከቱ የሚቋቋሙ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በሚመለከት ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብር ትናንት ሚያዝያ 29 ቀን 2005 ዓ.ም አካሄደ፡፡
በስልጠናው ወጣቶቹ ሰፊ ውይይትና ምክክር ያደረጉ ሲሆን በሁሉም አኅጉረ ስበከት ለማደራጀት ከማደራጃ መምሪያው ዘንድ ሲላኩ በምን ዓይነት ዘይቤ ሥራውን የተሳካ ማድረግ እንደሚገባቸውም የጋራ ስምምነትና መረዳት ደርሷል፡፡
የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዓመታዊ የወጣቶች መደበኛ ጉባኤ ለማካሄድ በከፍተኛ ዝግጅት ላይ ሲሆን ይህም አንዱ የጉባኤ አካል መሆኑ በዕለቱ ተገኝተው ስልጠናውንና የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብሩን የመሩ የመምሪያው ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የትንሣኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ያስተላለፉት ቃለ በረከት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
-
በሃገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ፣
-
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አኅጉር የምትኖሩ
-
የሀገራችን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ
-
በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ
-
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤
በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ያበሰረን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለ2005 ዓ.ም ለበዓለ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ፡፡
"እስመ ሐደሰ ለነ ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት ንቅረብ እንከ በልበ ጽድቅ" የሕይወትና የእውነት መንገድ አድሶልናልና ከእንግዲህ በቅን ልቡና ወደ እርሱ እንቅረብ" ዕብ.10፡19
የሰው ልጅ ለማያረጅና ለማያልፍ ሕይወት የታደለ፤ በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል የተፈጠረ እጅግ ክቡርና ታላቅ ፍጥረት እንደ ነበረ ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሰክራሉ፡፡ በምድር በሚገኙ ፍጥረታት ሁሉ ላይ ያለው የበላይነት ሥልጣንም ይህንን ያረጋግጣል፡፡
የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ዘንድ ይህን ያህል ጸጋ ቢኖረውም የተሰጠውን ክብርና ልዕልና በአግባቡ ጠብቆ መዝለቅ አልቻለም፡፡ በእግዚአብሔር ፊት በፈጸመው ከባድ በደል ምክንያት የተሰጠውን ጸጋና ክብር ከማጣቱም በላይ በሕይወት ፈንታ ሞትን በእውነት ፈንታ ሐሰትን፣ በዘለአለማዊነት ፈንታ ጊዜያዊነትን በማያረጀውን ፈንታ የሚያረጀውን ሕይወት ተላብሶ ወደ ምድረ ፍዳ ተባረረ፤ ከእግዚአብሔር ልጅነት ተራቆተ፤ ከማኅበረ መላእክት ተለየ፤ ረዳት የለሽና ጎስቋላ ሕይወት ተሸክሞ መኖር ጀመረ፡፡
"የሰንበት ትምህርት ቤት ከፍተኛ አመራሮች፣ የክፍለ ከተማ፣ የአዲስ አበባና የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤት አንድነት አመራሮች ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር ትውውቅና ቡራኬ ተቀበሉ"ከሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጀምሮ እስከ አጥቢያ ድረስ የሚገኙ የሰንበት ት/ቤት አመራሮች በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ አስተባባሪነት ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ቅዳሜ ሚያዝያ 12 ቀን 2005 ዓ.ም በጽ/ቤታቸው ተገኝተው ትውውቅ፣ ሰፊ የሥራ ምክክር እና አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ተቀበሉ፡፡ መርሐ ግብሩ ከመጀመሩ አስቀድሞ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ኃላፊ የሆኑት መምህር ዕንቈባሕርይ ተከስተ የወጣቶቹን ሁለገብ የፍቅር አገልግሎትና የማደራጃ መምሪያው ድጋፍ ሰፊ ገለጻ ካደረጉ በኋላ "አሁንም እንደ ትላንቱ ይህንን ወጣት የቤተ ክርስቲያኑ ድምጽ በመስማት እየታዘዘና ከልቡ እያገለገለ የሚገኝ ታማኝ አገልጋይ ነው" በማለት ስለወጣቶች አገልግሎት አብራርተዋል፡፡ በመቀጠልም ይህንን የፍቅር አገልግሎት ለማደናቀፍ የውስጥና የውጭ ፈተናዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተፈታተኑት መሆኑን አብራርተው ወጣቱ ግን ይህንን ሁሉ ችሎ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያኑ ታማኝ ሆኖ በጽናት በማገልገል፣ አጽራረ ቤተ ክርስቲያንም በመከላከል ላይ የሚገኝ የቤተ ክርስቲያን አለኝታ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ከሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮች ዲያቆን በላይ ገ/ሕይወት ንግግር ያደረገ ሲሆን ንግግሩ ያተኮረውም በሰንበት ት/ቤቶች አደረጃጀትና የአምስት ዓመት መሪ ዕቅድን በሚመለከት ነበረ፡፡ ሰንበት ት/ቤቶች ከማዕከል እስከ አጥቢያ ድረስ መዋቅራዊ ትስስር እና ከወረዳ እስከ መንበረ ፓትርያርክ ሀገር አቀፍ ድረስ ሕብረትና አንድነት ፈጥረው የተሻለ አገልግሎት እንዲያበረክቱና ሁሉም አንድ ዓይነት ተልዕኮ፣ ራዕይ፣ አገልግሎት ... እንዲኖራቸው ለማድረግ ሁሉንም ቅድመ ሁኔታዎች አልቀው ወደተግባር እየተገባ መሆኑን ገልጿል፡፡ ከአዲስ አበባ አንድነትም የአንድነቱ ሰብሳቢ ዲ/ን ሄኖክ አስራት የሰንበት ት/ቤቶች አገልግሎት መልክና ቅርጽ ይዞ ወጥ የሆነና የተሳካ ሁለገብ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል ከማደራጃ መምሪያው ጀምሮ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውንና ቅዱስነታቸውን ትኩረት ለወጣቱ በመስጠት አባታዊ ቡራኬያቸው ሁሌም እንዳይለየው አደራ ጭምር አብራርቷል፡፡ ቅዱስ ፓትርያርኩም የሁሉንም ንግግር ካዳመጡ በኋላ የወጣቱ ኃይል የቤተ ክርስቲያን የደም ሥር ስለሆነ ልዩ ትኩረትና እንክብካቤ ሊደረግለት ይገባል፡፡ ከዚህ የበለጠ የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮ አይኖርም፣ እንደአብነት ት/ቤቱ ሁሉ ለሰ/ት/ቤትም ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ያለው ተጠናክሮ የሚቀጥልበት መጨመር ያለበትን ዳግም ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ በማቅረብ አስፈላጊ ድጋፍና ክትትል እንዲደረግ አብረን እየተወያየን እየተመካከርን አገልግሎቱ የተሳካ ማድረግ ይኖርብናል በማለት ሰፊ አባታዊ ምክራቸውንና መመሪያቸውን ከሰጡ በኋላ ቡራኬ ሰጥተው በጸሎት መርሐ ግብሩን ዘግተውታል፡፡ ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መደበኛ ጉበኤ ለማካሄድ ቅድመ ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ አስታወቀየሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ወጣቶችን ከሀገር አቀፍ ከመንበረ ፓትርያርክ ጀምሮ እሰከ አጥቢያ ድረስ ልዩ ትስስር ፈጥረው የራሳቸው የሆነ አንድነትና ሕብረት መስርተው አንድ ሀገር አቀፍ ራዕይና ተልዕኮ ገንዘብ አድርገው የተሳለጠ መንፈሳዊ አገልግሎት እንዲመሩ ለማስቻል በቀድሞ ቅዱስ ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅዱስ ዶክተር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንትና የዓለም የሰላም አምባሳደር አማካኝነት በዓለ ጰራቅሊጦስን የሰንበት ት/ቤቶች ቀን በሚል በተሰየመው መሠረት ዘንድሮም ለሁለተኛ ጊዜ ሀገር አቀፍ መደበኛ ጉባኤ እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡ ማደራጃ መምሪያው የዚህ የመጀመሪያ የሆነ የጉባኤም "የምስረታ መደበኛ ጉባኤ" ተብሎ ባለፈው ዓመት ተካሂዶ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከሁሉም አኅጉረ ስብከቶች ተወካዮች በተገኙበት ሀገር አቀፍ መሪ ዕቅድ ረቂቁ ቀርቦ ከፍተኛ ውይይትና ምክክር ተካሂዶበት ከጉባኤተኞቹም እንደግብአት የሚያገለግሉ ተጨማሪ ሐሳቦች ቀርበውለት ለዘንድሮ ጸድቆ ሥራ ላይ እንዲውል ያለፈው ዓመት ቀጠሮ መያዙን አስታውሶ የዘንድሮ ዓመት መደበኛ ጉባኤ ግን ለየት ያለ ከመሆኑም በላይ ለሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ተልዕኮ መሠረት የሚጥል መሪ ዕቅድ ጸድቆ መመሪያ ለሁሉም አኅጉረ ስብከት ተላልፎ ሥራ የሚያስጀምር ጉባኤ መሆኑን ገልጿል፡፡ ይህንን መደበኛ ጉባኤ ሰኔ 15 እና 16 ቀን 2005ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን ጉባኤው የተሳካ እንዲሆንም አስፈላጊ የሆኑ ንዑሳን ኮሚቴዎች ተቋቁመው ሥራ መጀመራቸውን አስታውቋል፡፡ ዐቢይ ጾምና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትውፊትበመምህር ሙሴ ኃይሉ (B.TH, MA in philo) "ቀድሱ ጾመ … ቀድሱ ጾመ …" "ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ …" "ጾመ እግዚእነ ጾመ በእንቲአነ አርአያሁ ከመ የሀበነ" "ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ወንትፋቀር በበይናቲነ " "ዓይን ይጹም እምርእየ ሕሱም ዕዝን ይጹም እምሰሚዓ ሕሱም ልሳንኒ ይጹም እምተናግሮ ሕሱም " ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በተለያዩ መጻሕፍት እንደተጻፈውና በተለያዩ የቤተክርስቲያናችን መምህራን ሊቃውንት በየዓውደ ምሕረቱ እንደሚተነተነው ጾም ማለት በታወቀ፣ በተወሰነ፣ በተቀመረ…ጊዜ ከመብል ከመጠጥ መከልከል፣ መቆጠብ፣ መወሰን…ማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን “ጾም”ከክርስቲያናዊ ምግባርና ትሩፋት የሚመደብ ኣስተምህሮ ነው፡፡ ጾም የመሠረተውም ሆነ የታዘዘው ከፈጣሬ ሰማያት ወምድር ከእግዚአብሔር ነው፡፡ በመሆኑም ማንኛውም ምዕመን ጾምን በመከተል ለሠራዔ ጾም (ጾም ለሠራለት)አምላክ እየተገዛ፣ እያመለከ፣ እያከበረ፣ እየታዘዘ…በበጎ ሕሊና ተሞልቶ ፈቃደ ሥጋውን (ትዕቢት፣ ስስት፣ ዝሙት፣ ቅንዓት…) ለፈቃደ ነፍሱ (የዋህነት፣ በጎነት፣ ርህሩህነት…) በማስገዛት በፈጣሪ መመሪያ፣ ትእዛዝ መኖር ማለት ነው፡፡
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜንየብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የዐቢይ ጾም መልእክት
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የ2005 ዓ.ም መዋዕለ ጾም በሰላም አደረሳችሁ፡፡"እብለክሙ በመንፈስ ሑሩ ወፍትወተ ሥጋክሙ ኢትግበሩ"
|
- ራሱን "ቅዱስ ሲኖዶስ" ብሎ የጠራው አካል ያወጣውን የሐሰት መግለጫ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
- ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ6ኛው ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካህናት ምዕመናንና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ጥቆማ መስጠታቸውን ቀጥለዋል፤
- በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን
- በዓለ ጥምቀት
- ስለወቅታዊ ጉዳይ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
- በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ "በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዝክረ ቅዱስ ያሬድ" በሚል ጥር 5 ቀን 2005 ዓ.ም በተካሄደ ታሪካዊ ጉባኤ
- ብፁዕ አቡነ ናትናኤል አቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ2005 ዓ.ም በዓለ ልደትን ምክንያት አድርገው ያስተላለፉት ቃለ በረከት
- የአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን የትንቢት ቀጠሮ
- አእማደ ምስጢር

