ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ጉባኤ
ስማቸው
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ
ወላዲ ተወላዲ ሠራጺ
ልብ ቃል እንስትንፋስ
በአካል በግብር በከዊን ተለያይተው በህልውና ተገናዝበው በሦስትነት የሚጠሩበት የሦስትነት ስማቸው ነው፡፡
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ፣ በአካል ተለያይተው በሦስትነት የሚጠሩበት የአካል ስማቸው ነው፡፡
(ማቴ28፡19)
ወላዲ፣ ተወላዲ፣ ሠራጺ፣ በግብር ተለያይተው በሦስትነት የሚጠሩበት የግብር ስማቸው ነው፡፡
ይኸውም አብ ወላዲ፣ ወልድ ተወላዲ፣ መንፈስ ቅዱስ ሠራጺ ማለት ነው፡፡
ልብ ቃል እስትንፋስ በከዊን ተለያይተው በህልውና ተገናዝበው በሦስትነት የሚጠሩበት የከዊን ስማቸው ነው፣ ይኸውም ከዊነ ልብ ከዊነ ቃል ከዊነ እስትንፋስ ማለት ሲሆን በሌላ አገላለጽ አብ ልብ ወልድ ቃል መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ማለት ነው፡፡
የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ እንደቀጠለ ነውበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከሚካሄድባቸው አንዱ የሆነው የርክበ ካህናት ዓመታዊ መደበኛ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሐዋርያዊ ትውፊቱን ጠብቆ በልዩ ልዩ የቤተክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልዕኮ ላይ አትኩሮ በመልካም መንፈሳዊ ሥርዓት እንደቀጠለ ነው፡፡ የቅዱሰ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚዝያ 30 ቀን 2004ዓ.ም ከቀኑ በ10፡00ሰዓት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በጸሎት የተጀመረ ሲሆን አጀንዳዎቹን ለይቶ በመወያየት ካበቃ በኋላ እንደተለመደው በመጨረሻ የውሳኔ ሐሳቦቹ በይፋ ለሕዝብ በመግለጽ ይጠናቀቃል፡፡ የተከበራችሁ አንባቢዎቻችን የቅዱስ ሲኖዶስ የመዝጊያ መርሐ ግብር በድምጽ ወምስልና በጽሑፍ ይዘን እንቀርባለን፡፡ ዓሠርቱ ቀናት ለማኅበረ ቅዱሳንበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሥር ከሚገኙት በርካታ ማህበራት መካከል አንዱ ማኅበረ ቅዱሳን መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ማህበረ ቅዱሳን ከተቋቋመለት ዓላማ ውጭ በመሆን መንገዱን ስቶ መሄዱን በርካታ የማህበሩ አባላት እየገለጹ ከመሆናቸውም በላይ የማህበሩ አካሄድ ለቤተ ክርስቲያን ከባድ አደጋ እንደሆነ በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው፡፡ ለዚህ ደግሞ አንጋፋው የማህበረ ቅዱሳን መሥራች የነበረው መምህር በድረ ገጽ ላይ ሥውር አመራር እና ግልጽ አመራረ እያለ በመተንተን በሚገባ በማህበሩ ውስጥ የሚሠራውን ሴራ አስነብቦን እንደነበር ግልጽ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅትም የማህበሩ አካሄድ ከቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ሥር እያፈነገጠ ባለበት በዚህ ወቅት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሳይቀር የስህተት ምሳሌ ሆኖ መጠቀሱ ይታወሳል፡፡ እንግዲህ በዚህ የ20 ዓመት ጉዞው ውስጥ ማህበሩ በቤተ ክርስቲያን ስም እያመካኘ ነገር ግን ለራሱ የሚሠራ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ግን ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እያመዘነ መምጣቱን አንዳንድ ለቤተ ክርስቲያኒቱ የሚቆሙ የማህበሩ አመራር አባላት ይናገራሉ፡፡ ትተው እንዳይወጡ ደሞዝ እንዳይሰሩም ጭንቅ የሆነባቸው ወንድሞች በማህበረ ቅዱሳን ውስጥ በርካታ ናቸውና፡፡ ይህን የምንለው የማህበሩን አካሄድ አታውቁም ብለን ሳይሆን እናስታውሳችሁ ብለን ነው፡፡ የረሳችሁትን እንድታስታውሱ ስንል ያልሰማችሁትን ደግሞ እንድትሰሙ ፈቃዳችን ነው፡፡ ባሳለፍነው ወር ማለትም በሚያዝያ ወር ውስጥ በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊነት ተሰይመው የነበሩት መልዐከ ጽዮን አባ ኅሩይ ወንድይፍራው ተደርጎ የማይታወቅ ጉዳይ ይዘው ብቅ በማለታቸው ሳይሾሙ ተሻሩ፡፡ ጉዳዩ እንዲህ ነው፡፡ በማህበረ ቅዱሳን ጤናማ ያልሆነ አካሄድ ላይ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና የመንግሥት ሚኒስትሮች እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኒቱ ታላላቅ አመራር ተገኝተው መስከረም 12 ቀን 2002ዓ.ም ባለ 6 ነጥብ ውሳኔ አስተላልፈዋል፡፡ ያንን ውሳኔ ለማስፈጸም ማደራጃ መምሪያው ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ሲታገል ቆይቷል፡፡ ማህበረ ቅዱሳን ግን ለመፈጸም ፈጽሞ ፈቃደኛ ሊሆን አልቻለም፡፡ በመሆኑም በአሁኑ ሰዓት ከ10 ቀን ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የተወሰነውን ውሳኔ እንዲፈጽም ካልሆነ ግን አስተዳደራዊ እርምጃ እንወስዳለን የሚል ደብዳቤ እንዲጻፍ ይወሰናል፡፡ በወቅቱ አባ ኅሩይ አምነውበት ተቀብለው ከፈረሙበት በኋላ ሁለት ቀናትን አሳልፈው በመምጣት ደብዳቤውን ስላላመንኩበት አይወጣም በማለት ከመዝገብ ቤት ክብ ማህተም ነጥቀው ተሰውረው ነበር፡፡ በእርግጥ ይህ ዓይነቱ አካሄድ ከአንድ አባት የሚጠበቅ ጉዳይ አልነበረም፡፡ ይሁን እንጂ የቢሮ አሠራር ስለማያውቁ እና በወቅቱ ከማህበረ ቅዱሳን ጸሐፊ ከዲ/ን ሙሉጌታ ኃይለማርያም ባገኙት ምክር መልካም ነገር መስሏቸው አደረጉ፡፡ የማደራጃ መምሪያው ሰራተኞች ግን በወቅቱ እጅግ ተገርመው ጉዳዩን ይከታተሉ ነበር፡፡ ማህተሙ በተነጠቀበት ጊዜ ዲ/ን ሙሉጌታ ኃ/ማርያም በማደራጃ መምሪያው መኪና ከአባ ህሩይ ጋር ቢሮ ገብቶ ሲያበረታታ ነበር፡፡ አባ ህሩይ በዚህ ጊዜ ነው የማህበሩ ቀኝ እጅ መሆናቸው በጥርጥር ውስጥ የገባው፡፡ አባቶች ለማህበራት ሳይሆን ለቤተ ክርስቲያን ሲቆሙ ቤተ ክርስቲያንን በደሙ የዋጃት አምላክ አብሯቸው ይቆማል ነገር ግን ከማህበራት ጋር ሲቆሙ ገንዘብ ብቻ አብሯቸው ይቆማል ገንዘብ ደግሞ ሕይወት አይሆንም፡፡ እንግዲህ ከላይ እንደተገለጸው አንድ ሃይማኖትን ይጠብቃል ያስጠብቃል ብለን የምናምነው አባት በጣም ቀላል የሆነውን ለማህበረ ቅዱሳን መስተካከያ እና መታረሚያ የሚሆን ደብዳቤ መጻፍ ከፈራና ዋጋ መክፈል ካቃተው በቤተ ክርስቲያን የአመራር ቦታ ላይ መቀመጡ ምንም ዓይነት ጥቅም የለውም ማለት ነው፡፡ ስለሆነም ቦታውን ለቆ መሄድ አማራጭ የሌለው ምርጫ ነው፡፡ ይህንንም ምክንያት አድርገን እውነታውን ትረዱ ዘንድ መልዐከ ጽዮን አባ ኅሩይ ወንድይፍራው ፈርመውበት የነበረውንና ኋላ ግን የፈረምኩት አስገድደውኝ ነው ያሉትን ደብዳቤ እንዲሁም አሁን በአዲሱ የማደራጃ መምሪያው ዋና ኃላፊ በመ/ር ዕንቈባሕርይ ተከስተ ተፈርሞ የወጣውን ደብዳቤ ከዚህ በታች እንደሚከተለው አስቀምጠንላችኋል፡፡ መልካም ንባብ 1. መልዐከ ጽዮን አባ ኅሩይ ወንድይፍራው ፈርመውበት የነበረውንና ኋላ ግን የፈረምኩት አስገድደውኝ ነው ያሉትን ደብዳቤ PDF 2. በአዲሱ የማደራጃ መምሪያው ዋና ኃላፊ በመ/ር ዕንቈባሕርይ ተከስተ ተፈርሞ የወጣውን ደብዳቤ PDF መምህር ዕንቈባሕርይ ተከስተ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ኃላፊ ሆነው ተሾሙበጠቅላይ ቤተ ክህነት ከተቋቋሙት መምሪያዎች አንዱና የወጣቱን አገልግሎት የሚመራ መምሪያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ነው፡፡ ይህንን ታላቅ መምሪያ ለአያሌ ዘመናት በምክትል የመምርያ ኃላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩት መምህር ዕንቈባሕርይ ተከስተ የማደራጃ መምሪያው ዋና ኃላፊ በመሆን ሚያዝያ 26 ቀን 2004ዓ.ም መሾማቸውን ለመምሪያችን ከደረሰ ደብዳቤ ለመረዳት ችለናል፡፡ መምህር ዕንቈባሕርይ ተከስተ ወጣቶችን በሥነ ምግባር፣ በያሬዳዊ ዜማና በመሳሰሉት እሴቶች የበለጸጉና የቤተ ክርስቲያኒቷን ተረካቢ መልካም ትውልድ በማፍራት በኩል የማይናቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ የቤተክርስቲያን ባለሙያ መምህር ናቸው፡፡ አሁንም ይህንን ተግባራቸውን በሙሉ ኃላፊነት መቀጠል እንዲችሉ ተጠንቶ መፈቀዱ የበለጠ ለማገልገል እንደሚረዳቸው የተለያዩ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎች ገልጸዋል፡፡ እኛም መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው እንመኛለን:: ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የተጻፈላቸውን ደብዳቤ ከዚህ ቀጥለን አቅርበናል፡፡ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዓመታዊ አገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶችን ጉባኤ አዘጋጀየሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዘላቂነት ያለው አገር አቀፍ የስልጠናና የጉባኤ መርሐ ግብር ዝግጅትን በተመለከተ እንደገለጸው በመምሪያው መሪነት በተለይ የአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነትን ማዕከል ያደረገ ዓብይ ኮሚቴ ቀደም ሲል ተቋቁም መደበኛ ሥራውን እያከናወነ ከመሆኑም ባሻገር ንኡሳን ኮሚቴዎችንም እስከ አጥቢያ ድረስ ዘርግቶ ስልጠናውንና ጉባኤውን የተሳካ ለማድረግ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጿል፡፡ የመርሐ ግብሩን ይዘት በተመለከተም አገር አቀፍ ሥልጠናና ጉባኤ በአንድነት የሚካሄዱ መሆናቸውን ገልጾ ስልጠናው ግንቦት 25-26 ቀን 2004 ዓ.ም እንደሚሰጥና ከየአህጉረ ስብከቱ ተወክለው የሚመጡና ከአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት የተወከሉ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እስከ አንድ ሺህ እንደሚደርሱ ገልጾ ጉባኤው በ26 ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅና ሠራተኞች፣ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ምዕመናንና ምዕመናት በተገኙበት እንደሚካሄድ ከወጣው መርሐ ግብር ለመረዳት ተችሏል፡፡ ከሆሣዕና እስከ ትንሣኤበመምህር ዕንቈባሕርይ ተከስተ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ በዛሬ ዝግጅታችን ትምህርተ ሃይማኖት የሚል ነው፡፡ ይህም ሆሣዕና ማለት ምን ማለት ነው? ዕለቱን በየዓመቱ እናከብረዋለን፤ ምን የተደረገበት ነው? የሰሙነ ሕማማት ምሥጢር ምንድን ነው? በጸሎተ ሐሙስ የተፈጸመው ሥርዓትስ፤ የዕለተ ዓርብ ታምራት፣ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ስለሚባለው፤ ጌታ በመቃብር ስለቆየበት የሰዓት አቈጣጠር፣ እንዲሁም ጌታ "ወይቤ ተፈጸመ ኲሉ" ያለበት ምክንያት ምንድነው? ቅዳሜ ሥዑር የተባለበት ምክንያትስ ዋና ትርጉሙ ምን ይመስላል? ትንሣኤ ክርስቶስና ትንቢቱ፣ የሚሉና የመሳሰሉ ነጥቦችን ነው፡፡ በዚህም መሠረት ከእኛ የሚጠበቀው የቤተ ክርስቲያንዋን ትምህርተ ሃይማኖት በጥንቃቄ ማቅረብ ሲሆን ከአንባቢው የሚጠበቀው ደግሞ ጽሑፉን በጥንቃቄ አንብቦ ማወቅና መረዳት ነው፡፡
ከቀድሞው የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዋና ኃላፊ በአሁኑ ጊዜ የትምህርትና ማሠልጠኛ መምርያ ዋና ኃላፊ ከሆኑት ከቆሞስ አባ ሠረቀብርሃን ወ/ሳሙኤል ጋራ የተደረገ ቃለ መጠይቅቆሞስ አባታችን ለቃለ መጠይቁ ፈቃደኛ ስለሆኑ እጅግ በጣም እናመሰግናለን ዝግጅት ክፍሉእንደሚታወቀው የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያን ላለፉት 6 ዓመታት መምራትዎ ይታወቃል፡ በዚህ ጊዜ የነበሩበትን የአገልግሎት ዘመን እንዴት ነው የሚገልጹት? በመምሪያው ለዚህ ያህል ዓመት የተሠሩት ዋና ዋና ሥራዎች ምን ምን ናቸው?ሥራዎቹን ለመሥራት ያጋጠሙ ፈተናዎች እና የተሰጡ መፍትሔዎች ምን ምን ናቸው? ቆሞስ አባ ሠረቀብርሃንከሁሉ አስቀድሜ ይህችን ሰዓት ባርኮ ቀድሶ ሰጥቶ ከእናንተ ከመንፈሳዊያን ወንድሞቼ ጋራ ይህንን ቃለ መጠይቅ ለመመለስ ለፈቀደልኝ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው እያልኩ እንዲሁም ደግሞ ለእናንተ ምንም እንኳ የጋራ ሥራችን ቢሆንም መልካም ሥራ መሥራት ይገባናል ብላችሁ የህን ቃለ መጠይቅ ስላደረጋችሁልኝ በእጅጉ በእግዚአብሔር ስም አመሰግናለሁ፡፡ ይህን ካልኩ ዘንድ ወደ ቀረበው ጥያቄ ልመለስና እርግጥ ነው ይህን ሁላችሁም እንደምታውቁት ለ6 ዓመታት ያህል በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጀ መምሪያ በተላላኪነት ወይም ደግሞ በሌላ አባባል በኃላፊነት በአገልግሎት ቆይቻለሁኝ፡፡ ስለዚህ በዚህ ባሳለፍናቸው 6 ዓመታት ውስጥ ሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ ሥራ ላይ መቼም ከባድ ወቅት ማለት ይቻላል ፈተና የበዛበት ነበር ማለት ይቻላል፡፡ በአንጻሩ ደግሞ በርካታ ሥራዎች የተከናወኑበት ለውጥ የታየበት ወቅት ነው ማለት ይቻላል፡፡ እና በዚህ 6 ዓመት የሰንበት ት/ቤት ቆይታዬ አሁን ሆኜ ስመዝነው ያሳለፍኩትን ሁኔታ ጠቅለል አድርጌ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ቀላል አይደለም ብዙ ፈተናዎችን አልፈናል ብዙ ሥራዎችንም ለመሥራት ችለናል፡፡ ከነዚያም መጀመሪያ እንደመጣሁኝ ከሥራ ባልደረቦቼ ጋራ በመሆን የማደራጃ መምሪያውን አቅም ለማጎልበት ማደራጃ መምሪያው የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ በሥርዓቱ እንዲወጣ ለማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ለማደራጃ መምሪያውና በማደራጃ መምሪያው ሥር ለሚንቀሳቀሱ ማንኛውም ለሁሉም ለሚመለከታቸው ማኅበራትም በተሰጣቸው ኃላፊነት ወይም ደግሞ ፈቃድ እንዲንቀሳቀሱ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል፡፡ በዚህ ሂደትም ብዙ ለውጥ አይተናል፡፡ ስለዚህ ከመጀመሪያው ይህንን ነው የማስታውሰው ማለት ነው፡፡ በሁለተኛው ስናየው ግን በዚህ በምንሠራቸው ሥራዎች ያጋጠሙ ችግሮች እና ችግሮቹን ለመፍታት የተወሰዱ መፍትሔዎች ወደሚለው እሄዳለሁ፡፡ ሰው መቼም በየትም ቦታ እስከ ሰራ ድረስ ሥራ እሰከጀመርክ ድረስ ችግር ያጋጥማል፡፡ ሰንበት ት/ቤት ማደራጃ መምሪያ እንደጥንቱ እንደፊተኛው ምንም ዓይነት ብዙ ተግባር ሳይኖር እንዲሁ በቀላሉ እያየ ብዙ ባይራመድ ኑሮ ጸጥ ብሎ ማለፍ ይቻላል፡፡ ብዙ ፈተናም አይገጥምም ነበር፡፡ ስለዚህ በዚህ ሂደታችን የገጠመን በአራት አቅጣጫ ነው ችግር ሲገጥመን የነበረ ሰዎች አብዛኛውን የሚያዩት የማኅበረ ቅዱሳንና የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ብቻ ነው የሚመስላቸው ችግራችን የነበረው ወይም ጎልቶ የታየው የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የማኅበረ ቅዱሳን ሲሆን ወይም ደግሞ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ እና የማኅበረ ቅዱሳን በሁለቱ መካከል ያለው ችግር ተብሎ ጎልቶ ይታይ ነበር፡፡ በመሠረቱ ግን ማደራጃ መምሪያ ገጥሞት የነበረው ቸግር በአራቱም አቅጣጫ ነበር፡፡ ከጠቅላይ ቤተክህነት ጀምሮ ራሱ ችግር ነበረበት፤
የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በቅዱስ አባታችን የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት የግብፁ አምባሳደር ሙሐመድ እድሪስ በመንበረ ፓትርያርክ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተገኝተው ያደረጉት ንግግርና የቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ በረከት በድምጽ ወምስል እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡ ቅዱስ ፓትርያርኩ የ2004ዓ.ም የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ በመላው ዓለም ለሚገኙ ምዕመናን ያስተላለፉት ቃለ በረከትበስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
|
- የአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን የትንቢት ቀጠሮ
- የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ከአዲስ አበባ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጋር በጥምቀት በዓል አከባበር ዙርያ ምክክር አካሄደ
- በስብከተ ወንጌልና ሐዋያዊ ተልዕኮ መምሪያ የተዘጋጀ የሦስት ቀን ሀገር አቀፍ የሠላም ጉባዔ ተጠናቀቀ
- ለአክሱም ጽዮን ያልተዘረጉ እጆች ለማን ይዘረጋሉ??
- የአክሱም ጽዮን የሙዝየም ሥራ በቅዱስ ፓትርያርኩና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም በከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት ተጐበኘ
- ታህሳስ 3 ቀን በዓታ ለማርያም ድንግል
- በሃይማኖት ጉዳይ የተሳሳተና ሚዛናዊ ያልሆነ መረጃ መስጠት ይቁም፡፡
- የመላእክት ተራዳኢነት
- የበገና አገልግሎት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን
- ያልተጠመቁ አጥማቂያን


