ትምህርተ ሃይማኖት
ዐቢይ ጾምና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትውፊትበመምህር ሙሴ ኃይሉ (B.TH, MA in philo) "ቀድሱ ጾመ … ቀድሱ ጾመ …" "ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ …" "ጾመ እግዚእነ ጾመ በእንቲአነ አርአያሁ ከመ የሀበነ" "ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ወንትፋቀር በበይናቲነ " "ዓይን ይጹም እምርእየ ሕሱም ዕዝን ይጹም እምሰሚዓ ሕሱም ልሳንኒ ይጹም እምተናግሮ ሕሱም " ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በተለያዩ መጻሕፍት እንደተጻፈውና በተለያዩ የቤተክርስቲያናችን መምህራን ሊቃውንት በየዓውደ ምሕረቱ እንደሚተነተነው ጾም ማለት በታወቀ፣ በተወሰነ፣ በተቀመረ…ጊዜ ከመብል ከመጠጥ መከልከል፣ መቆጠብ፣ መወሰን…ማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን “ጾም”ከክርስቲያናዊ ምግባርና ትሩፋት የሚመደብ ኣስተምህሮ ነው፡፡ ጾም የመሠረተውም ሆነ የታዘዘው ከፈጣሬ ሰማያት ወምድር ከእግዚአብሔር ነው፡፡ በመሆኑም ማንኛውም ምዕመን ጾምን በመከተል ለሠራዔ ጾም (ጾም ለሠራለት)አምላክ እየተገዛ፣ እያመለከ፣ እያከበረ፣ እየታዘዘ…በበጎ ሕሊና ተሞልቶ ፈቃደ ሥጋውን (ትዕቢት፣ ስስት፣ ዝሙት፣ ቅንዓት…) ለፈቃደ ነፍሱ (የዋህነት፣ በጎነት፣ ርህሩህነት…) በማስገዛት በፈጣሪ መመሪያ፣ ትእዛዝ መኖር ማለት ነው፡፡
|
በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህንበመ/ር ዕንቈባሕርይ ተከስተ "ወይቤሎ መንፈስ ቅዱስ ለፊልጶስ ሑር ወትልዎ ለዝንቱ ሠረገላ ወሮጸ ፊልጶስ ወበጽሐ ወስምዖ ያነብብ መጽሐፈ ኢሳይያስ ነቢይ ወይቤሎ ፊልጶስ ተአምርኑ እንከ ዘታነብብ፡፡ ወይቤሎ ኀፅው በአይቴ አአምር ለእመአልቦ ዘመሀረኒ"፡፡ "መንፈስ ቅዱስ ፊልጶስን ይህን ሠረገላ ሂድና ተከተለው አለው፡፡ ፊልጶስም ሮጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰማውና በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን አለው ጀንደረባውም የሚያስተምረኝ ሳይኖር ይህ እንዴት አውቀዋለሁ አለው፡፡" (የሐዋ.ሥራ ም.8፥29-32) እኛም ሆነ ሌላው የክርስትና ዓለም እንደሚያውቀው ኢትዮጵያ በመጽሐፍ ቅዱስ የታወቀች ሀገር እንደሆነች ብዙ ነቢያት በትንቢታቸው አንስተዋታል፡፡ በጽሑፋቸውም በብዕራቸው ደጋግመው ቀልመዉታል፡፡ ኢትዮጵያ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ከ45 ጊዜ በላይ ስምዋ የተጠቀሰ ሲሆን ከክርስትና እምነት በፊት ማለትም በብሉይ ኪዳን ዘመን በአንድ አምላክ ታምን እንደ ነበረ በብዙ ቦታ ተጠቅሳለች፡፡ በተለይ ከ1013 - 982 ቅድመ ልደተ ክርስቶስ የነበረችው የኢትዮጵያ ንግሥት ማክዳ /ንግስተ ሳባ/ የሰሎሞንን ጥበብና ዜና ለማየት በዘመኑ የነበረው የኢትዮጵያን ሥልጣኔ ለማስተዋወቅ የብሉይ ኪዳንንም እምነትና ሥርዓትን ትምህርቱን ከመሠረቱ ለመረዳት ወደ ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም መሄድዋን በመጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ ምዕ.10 ቁ.1-12፡፡ በዜና መዋዕል ካልእ.ምዕ.9 ቁ.1‐12 ተመዝግቦ ስለሚገኝ የታሪክ እውነትነቱን ያረጋግጧል፡፡ ንጉሥ ሰሎሞንም ለኢትዮጵያ ንግሥት ማክዳ የወደደችውን ሁሉ እንደሰጣት መጽሐፍ ቅዱስ ይገልጻል፡፡
ምሥጢረ ሥጋዌ፤ምሥጢረ ሥጋዌ የሚባለው ትምህርተ ሃይማኖት፤ ቃል ሥጋ ኾነ ብለን የምናምነው እምነት፤ ቃል ሥጋ ኾነ ብለን የምንማረው ትምህርት ነው፡፡ በምሥጢረ ሥላሴ ትምህርት እናምናለን በአብ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ ባንድ አምላክ በማለት እምነታችንን መግለጻችን ይታወሳል፡፡
ማስገንዘቢያ፡-ሰው ሆነ ያልነው ወልድ፣ ዮሐንስ ወንጌላዊ "ቃል ሥጋ ኮነ" ያለው አካላዊ ቃል ነው፡፡ አካላዊ ቃል ወልድ ሰው ሲሆን ሳለ መለኮቱ እና ትስብእቱ /ሰውነቱ/ አንድ አካል አንድ ባህርይ ሁኗል፡፡ ሁለት አካል፣ ሁለት ባሕርይ አይባልም ወይም አንድ አካል ሁለት ባህርይ አይባልም፡፡ ምንታዌ የለበትም፣ በተዋሕዶ ወልደ አብ ወልደ ማርያም ሁኗል ወልደ አብ ወልደ ማርያም ነው፡፡
የአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን የትንቢት ቀጠሮከመምህር ዕንቈ ባሕርይ ተከስተበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ኃላፊ
ዝርዝር ሐተታ ከመሄዳችን በፊት ገና ማለት ምን ማለት እንደሆነ ትርጉሙ እነሆ፡፡ ገና ማለት ከጽርዕ /ግሪክ/ ቋንቋ የተወረሰ ነው፡፡ ትርጉሙም ልደት ማለት ነው፡፡ እንደሚታወቀው ሁሉ አዳም አባታችን ወዶ በሠራው ኃጢአት ምክንያት የዓለም መድኅን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ተወለደበት ጊዜ ድረስ ዓለም በጨለማ ጒዞ ይጓዝ ነበር፡፡ /ኢሳ. 9፡2/ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተወለደ በኋላ ግን በጨለማ ጥላ ሥር ይንከራተትና ፍዳውን ይቈጥር ይኖር የነበረ ሕዝብ ብርሃን አየ፤ ተስፋ ያልነበረው ሕዝብ የተስፋ ባለቤት ሆነ፣ የጨለማና የኀዘን የሥቃይ፣ የፍዳ፣ የገፊና የተገፊ መናኸሪያ የነበረው አሮጌው ዓለም በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ዓለም ሆኗል፡፡ /ኢሳ. 9፡2፣ ሮሜ.13፡12/
ክፍል ሁለትአእማደ ምስጢርበብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ ሊቀ ጳጳስ
|
- መስቀል ብርሃን ለኩሉ ዓለም
- ለመሆኑ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም ትባላለችን?
- ለመሆኑ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም "መድኃኒተ ዓለም" ትባላለችን?... ለምን?
- "ፍልሰታ ለማርያም ደንግል ወላዲተ አምላክ" ካለፈው የቀጠለ
- "ፍልሰታ ለማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ"
- መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ
- "እጃችሁን ለእግዚአብሔር ስጡ" (፪ዜና ፴፥፰)
- "በዐለ ሐምሳ"
- ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ጉባኤ
- ከሆሣዕና እስከ ትንሣኤ
1. ስለ መሲሑ የዓለም መድኅን ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድና የበዓሉ አከባበር፤
"ጽጌ አስተርአየ ሰሪፆ እምአጽሙ