የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ሲመት
|
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስድስተኛው ፓትርያርክ ምርጫ ብፁዕ አቡነ ማቲያስን በምምረጥ ተጠናቋል።ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ በ 12 ሰዓት ጅምሮ ብፀዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የመምሪያ ሓላፊዎች፤ የሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆችና ሌሎችም በቅደም ተከተል በተገኙበት የመራጭነት ቃለ መሓላ ከፈጸሙ በኃላ በሊቃነ ጳጳሳቱ መሪነት ምርጫው በጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ውስጥ በሰላማዊ እና ሐዋርያዊ ትውፊቱን በጠበቀ መንገድ ከ806 ድምጽ 500 ድምጽ በማግኝት ብፁዕ አቡነ ማቲያስ ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ሆነው መመረጣችወን በይፋ ተገልጾል።
ዝርዝር ዜናውን ተከታትልን እንድምናቀርብ ከወዲሁ እንግልጻልን። የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ልዑካን በጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተገኝትው ድምጽ ሰጡ።የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ጋራ ባላት ስምምነት መሠረት አምስት ድምጽ ሰጪዎች በዛሬው ዕለት የ6ኛ ፓትርያርክ ምርጫ ላይ በጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተገኝትው ህጉ በሚፈቅድላችው መሠረት አምስቱ ልዑካን የምርጫ ካርዳችውን በመውሰድ ድምጻቸውን ሰጥትዋል። ከድምጽ ሰጪዎቹ መካከል ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ሲሆኑ ሁለቱ ደግሞ የቤተክርስቲያኒቱ ከፍተኛ ሃላፊዎች ናቸው። ከምርጫው አስቀድሞ ከግብፅ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ልዑካን ድምጽ ሰጪዎች መካከል አንድ አባት ሰፊ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራችው "እኛ ከግብፅ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ የመጣነው ድምጽ ለምስጠት ብቻ ሳይሆን ከኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችን ጋር ጎን በመሆን ለዚህች ለተቀደሰች ቤ/ክ እግዚአብሔር መልካም እረኛ እንዲሰጣት ለመጸለይም ጭምር ነው፤እኛ ከግብፅ የቅዱስ ማርቆስን በረከትን ይዘንላችሁ መጥተናል፤ ከዚህም ደግሞ የቅዱስ አባታችን አቡነ ተ/ሃይማኖትን በረከት ይዘን እንሄዳለን፤ መንፈሳዊ ምርጫ ለመንፈሳዊ አገልግሎት ነው በመሆኑም ይሄንን ሃላፊነት የሚሸከም አባት እግዚአብሔር ለዚህች እህት ቤ/ክ እንዲሰጣት ተነሱና አብረን እንጸልይ" በማለት ጸሎት አድርገዋል። በመቀጠልም አምስቱ ልዑካን የመረጡ ሲሆን ታዛቢዎችም በተዘጋጀላቸው ቦታ ላይ ሆንው በመታዘብ ላይ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ የ6ኛ ፓትርያርክ ምርጫ እየተካሄደ ነው።ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም ከጠዋቱ በ 12 ሰዓት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ከየአሃጉረ ስብከቱ የመጡ ተወካዮች በተገኙበት የመራጭነት ቃለ መሓላ ከፈጸሙ በኃላ በሊቃነ ጳጳሳቱ መሪነት ምርጫው በጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ውስጥ ሐዋርያዊ ትውፊቱን በጠበቀ መለኩ በሰላማዊ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል።
የስድስተኛው ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም ዕጩ ፓትርያርኮችን አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በተገኙበት ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም የአምስቱ ዕጩ ፓትርያርኮች ስም ዝርዝርና የምርጫ ሁኔታውን አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡ አሰመራጭ ኮሚቴው በመግለጫው እንደገለጸው አስቀድሞ ለምዕመኑ በተላለፈው ጥሪ መሠረት ጥቆማ ማካሄዱን ገልጾ ይህንን ጥቆማ እንደግብአት በመጠቀም የምርጫ ሕጉ መሠረት በማድረግ ሰፊ ምክክርና ጥልቅ ውይይት ከተደገረ በኋላ አምስት አባቶችን መርጦ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አቅርቦ ምልዓተ ጉባኤው በአስመራጭ ኮሚቴው የቀረቡ አባቶች በሙሉ ተቀብሎ በማሳለፉ ምክንያት ዛሬ ስማቸው ለሕዝብ በይፋ ለሕዝብ ለመግለጽ በቅተናል ብሎአል፡፡ የዕጩ ፓትርያርኮቹ ስም ዝርዝር፡-
2. ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ 3. ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል 4. ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ 5. ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ መሆናቸውን ይፋ አድርጎአል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ያስተላለፈውን ሙሉ መግለጫ ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቦአል፡፡
የስድስተኛው ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም ዕጩ ፓትርያርኮችን አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በተገኙበት ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም የአምስቱ ዕጩ ፓትርያርኮች ስም ዝርዝርና የምርጫ ሁኔታውን አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡ አሰመራጭ ኮሚቴው በመግለጫው እንደገለጸው አስቀድሞ ለምዕመኑ በተላለፈው ጥሪ መሠረት ጥቆማ ማካሄዱን ገልጾ ይህንን ጥቆማ እንደግብአት በመጠቀም የምርጫ ሕጉ መሠረት በማድረግ ሰፊ ምክክርና ጥልቅ ውይይት ከተደገረ በኋላ አምስት አባቶችን መርጦ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አቅርቦ ምልዓተ ጉባኤው በአስመራጭ ኮሚቴው የቀረቡ አባቶች በሙሉ ተቀብሎ በማሳለፉ ምክንያት ዛሬ ስማቸው ለሕዝብ በይፋ ለሕዝብ ለመግለጽ በቅተናል ብሎአል፡፡ የዕጩ ፓትርያርኮቹ ስም ዝርዝር፡-
2. ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ 3. ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል 4. ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ 5. ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ መሆናቸውን ይፋ አድርጎአል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ያስተላለፈውን ሙሉ መግለጫ ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቦአል፡፡
ራሱን "ቅዱስ ሲኖዶስ" ብሎ የጠራው አካል ያወጣውን የሐሰት መግለጫ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"ኢያስሕቱክሙ አኃዊነ ፍቅራን፤
|
- ሞት ላይቀር እውነት እንናገር
- በግብፅና በኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ትብብር በምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሰፊ ጉባኤ ተጀመረ
- ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
- መደበኛ የጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ተጀመረ
- ከጥቅምት 6-11 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም. ድረስ ለሚካሔደው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 31ኛ ዓመታዊ ስብሰባ ስለ 2ዐዐ4 በጀት ዓመት የሥራ ክንውን የቀረበ አጠቃላይ ዘገባ/ሪፖርት/
- 31ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዛሬ ተጀመረ
- በየዓመቱ የሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ዘንድሮም በታላቅ ድምቀት ተከበረ፡፡
- የቅዱስ ፓትርያርኩ ዜና ሕይወት
በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተቋቋመው የስድስተኛው ፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ የምርጫውን ሂደት በተመለከተ ጥር ሰላሳ ቀን 2005 ዓ.ም አጠቃላይ መግለጫ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫም የሚዲያ ተቋማት መልእክቱን ለሕዝብ እንዲደርስ ስላደረጋችሁ በቤተ ክርስቲያናችን ስም እናመሰግናለን፡፡